የቡና ምርታማነትን ማሳደግ
Back

የቡና ምርታማነትን ማሳደግ

ECTA
5 min read

የቡና ምርታማነትን በማሳደግ ከዘርፉ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ የቡናና ቅመማ ቅመም ጽ/ቤት ገለፀ፡፡

ወራቤ፤ ታህሳስ 26/2018 ስልጤ ኤፍ ኤም፤ የቡናና ቅመማ ቅመም ልማት ጽ/ቤት በቡና ወቅታዊ ተግባራት ዙሪያ ለወረዳና ከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች የክህሎት ስልጠና ሰጥቷል፡፡

ያረጀ ቡና ጉንደላና ምቀሳ እንዲሁም በተከላ ቡና ቅየሳ አወጣጥና በቡና ችግኝ አተካከል ፣በቡና በሽታና በግብይት መመሪያ ዙሪያ በጽ/ቤቱ ከፍተኛ ባለሙያዎች ተሰጥቷል፡፡

በስልጠና ማጠቃለያ ላይ የዞኑ ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊና የቡና ቅመማ ቅመም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቶፊቅ ኑሪ ስልጠናው የዘርፉ ባለሙያዎች በእውቀትና በክህሎት ታግዘው አርሶ አደሩን እንዲደግፉ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን አስገንዝበዋል።

ለቡና ምርታማነት መቀነስ ዋናው ምክንያት የቡና ማሳ አያያዝና እንክብካቤ ያለው አንዱ ጉድለት መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

በእርጅና ምክንያት ምርታማነታቸው የቀነሱ የቡና ዛፎችን ሳይንሱን ተከትለው ለማደስ እና ለመጎንደል የሚያስችል በንድፈ ሀሳብና በተግባር የተደገፈ ስልጠና ለአመራሮችና ለዘርፉ ባለሙያዎች መሰጠቱን አቶ ቶፊቅ ተናግረዋል፡፡

የቡና ምርታማነት በሁለት መንገድ ማሳደግ ይቻላል ያሉት አቶ ቶፊቅ አንደኛው ያረጁ ቡናዎች በማደስ (በመጎንደል) ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ያረጁ ቡናዎችን በንቀል በአዲስ መተካት እንደሆነ አስረድተዋል ።

ጉንደላ እና እድሳት የሚደረግላቸው ቡናዎች በተለይ በበሽታ የተጠቁ፣ ምርት መስጠት የማይችሉና እንዲሁም ከተተከሉ ረጅም ዕድሜ የሆናቸው እንደሆነም ኃላፊው አያይዘው ተናግረዋል።

አቶ ቶፊቅ አክለውም የቡና ምርታማነትን በማሳደግ ከዘርፉ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በዞኑ በዘንድሮ ዓመት ከ272 ሄክታር መሬት በላይ ቡናን ለመጎንደል ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

በስልጠናው የተሳተፉ አካላት ከቅየሳ ጀምሮ እስከ የቡና የተከላ አይነት፣ ጎንደላ፣ ምቀሳ እና ግረዛ ድረስ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የተደገፈ ግልፅና አስተማሪ የሆነ ግንዛቤ የተገኘበት እንደሆነ አንስተዋል፡፡

በመጨረሻም ያረጀ ቡና ጉንደላና ምቀሳ እንዲሁም በቡና ጉድጓድ ቁፋሮ ቅየሳ አወጣጥና በቡና ችግኝ አተካከል

በወራቤ ከተማ 01 ቀበሌ ወርኮ መንደር በአርሶ አደር የቡና ማሳ ላይ በተግባር የተደገፈ ስልጠና በመስጠት ተጠናቋል፡፡

Gallery

Gallery image 1
Gallery image 2
Gallery image 3
Gallery image 4

Tags

#ECTA#coffee